Alte pictures

Alte pictures Welcome To Our Page. I Like Captures Photo More in Natural Photo. in this page Natural Photos & Othe

የኤሌክትሪክ መኪና በኢትዮጵያ፡ ከውበቱ በስተጀርባ ያሉ መራራ እውነታዎችበኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪና (EV) ለመግዛት ከወሰኑ፣ ከውበቱና ከዘመናዊነቱ በስተጀርባ ያሉትን እነዚህን አስፈሪ የገ...
12/08/2026

የኤሌክትሪክ መኪና በኢትዮጵያ፡ ከውበቱ በስተጀርባ ያሉ መራራ እውነታዎች

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ መኪና (EV) ለመግዛት ከወሰኑ፣ ከውበቱና ከዘመናዊነቱ በስተጀርባ ያሉትን እነዚህን አስፈሪ የገንዘብና የቴክኒክ ስጋቶች አስቀድመው ሊያውቋቸው ይገባል፤

1. የባትሪው አስፈሪ ወጥመድ፡ በአንድ ጊዜ ከ$10,000 ዶላር በላይ!

ቀስ በቀስ መክፈል vs በአንድ ጊዜ መክፈል፡ የነዳጅ መኪና ሲነዱ የነዳጅ ወጪን በየሳምንቱ አነስተኛ ገንዘብ እየከፈሉ በሂደት ይሸፍናሉ። የኤሌክትሪክ መኪና ግን ባትሪው ሲያልቅ ወይም ሲበላሽ ቢያንስ 10,000 ዶላር (ከ1.6 ሚሊዮን ብር በላይ) በአንድ ጊዜ በጥሬ ገንዘብ መክፈል ይጠይቃል።

አዲስ መኪና እንደመግዛት፡ ከጥቂት ዓመታት አገልግሎት በኋላ የባትሪው አቅም ሲቀንስ፣ አዲስ ባትሪ ለመቀየር የሚወጣው ወጪ የመኪናውን አጠቃላይ ዋጋ እኩሌታ ይሸፍናል።

2. የኤሌክትሮኒክስ እና የመለዋወጫ (Accessories) ውድነት

የእቃ እጥረትና ውድነት፡ የኤሌክትሮኒክስ ክፍሎች፣ ስክሪኖች፣ ሴንሰሮች እና የውጭ አክሰሰሪዎች በአገር ውስጥ አይገኙም። ለማስመጣት በውጭ ምንዛሬ (Forex) እጥረት ምክንያት ከፍተኛ ወጪና ወራትን የሚወስድ ረጅም ጊዜ ይጠይቃል።

የባለሙያ እጥረት፡ በኢትዮጵያ የከፍተኛ ቮልቴጅ (High-Voltage) የኤሌክትሪክ ሲስተም እና የባትሪ ሞጁሎችን የሚያስተካክሉ በቂ ባለሙያዎችና ጋራዦች አለመኖራቸው የጥገና ወጪውን የበለጠ ያናረዋል።

3. የቻይና ኤሌክትሪክ መኪኖች ተጨባጭ ድክመቶች

የፋብሪካ ዋስትና (Warranty) ማጣት፡ አብዛኞቹ የቻይና ኤሌክትሪክ መኪኖች በኦፊሴላዊ ወኪል ሳይሆን በደላላ ወይም በግራጫ ገበያ (Grey Market) ስለሚገቡ ምንም ዓይነት የፋብሪካ የባትሪ ወይም የቴክኒክ ዋስትና የላቸውም።

የሶፍትዌር እና የቋንቋ እግድ፡ በርካታ የቻይና መኪኖች ሶፍትዌር በቻይና ቋንቋ የተቆለፈ ነው፤ አፕዴት (Update) ማድረግ አይቻልም፣ አልፎ አልፎም ስክሪናቸው ሙሉ በሙሉ በመቆለፍ መኪናው እንዳይንቀሳቀስ ያደርጋል።

የዳግም ሽያጭ ዋጋ (Resale Value) ውድቀት፡ ባትሪው እየደከመ ሲሄድ መኪናውን በሁለተኛ እጅ (Used car) የሚገዛዎ ሰው ማግኘት እጅግ ፈታኝ ይሆናል፤ የመኪናው ዋጋም በከፍተኛ ሁኔታ ይወርዳል።

4. የመሠረተ ልማት እና የኃይል ፈተናዎች

የመብራት መቆራረጥ፡ አገር ውስጥ ባለው የመብራት መቆራረጥ ምክንያት መኪናዎን በወቅቱ ቻርጅ ማድረግ አለመቻል ለዕለት ተዕለት እንቅስቃሴዎ ትልቅ እንቅፋት ይሆንብዎታል።

ከአዲስ አበባ ውጭ መሄድ አለመቻል፡ ከከተማ ውጭ በቂ የፈጣን ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች (Charging Stations) ባለመኖራቸው ምክንያት መኪናውን ለረጅም መንገድ ጉዞ መጠቀም አይቻልም።

Here we go! 💍❤️ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና የረጅም ጊዜ አጋሩ ጆርጂና ሮድሪጌዝ ከ10 ዓመታት የፍቅር ጉዞ በኋላ በይፋ በጋብቻ ተጣመሩ!ሮናልዶ የጋብቻ ቀለበታቸውን የሚያሳየውን ምስል አጋ...
11/08/2026

Here we go! 💍❤️

ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና የረጅም ጊዜ አጋሩ ጆርጂና ሮድሪጌዝ ከ10 ዓመታት የፍቅር ጉዞ በኋላ በይፋ በጋብቻ ተጣመሩ!

ሮናልዶ የጋብቻ ቀለበታቸውን የሚያሳየውን ምስል አጋርቷል።

ከ10 ዓመታት አብሮነት በኋላ አሁን በይፋ ባል እና ሚስት ሆነዋል!

ለአዲሶቹ ጥንዶች መልካም የጋብቻ ዘመን እንመኝላቸዋለን!

ክህደት መጨረሻው ውድቀት ነው!"የሲዳማን ህዝብ ልያዋሪዱ የሚተጉ ይጠፋሉ ።
07/08/2026

ክህደት መጨረሻው ውድቀት ነው!"

የሲዳማን ህዝብ ልያዋሪዱ የሚተጉ ይጠፋሉ ።

የኦሮሞ ሕዝብ ልዩነቶች ቢኖሩትም እንደቤተሰብ ይመክራል እንጅ ለፖለቲካ ሴራ አይጋለጥም  - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሞ ሕ...
07/08/2026

የኦሮሞ ሕዝብ ልዩነቶች ቢኖሩትም እንደቤተሰብ ይመክራል እንጅ ለፖለቲካ ሴራ አይጋለጥም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሞ ሕዝብ ልዩነቶች ቢኖሩት እንኳን እንደቤተሰብ ይመክራል እንጅ ለፖለቲካ ሴራ መጋለጥ የለበትም አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኦቢኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ÷ የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄዎች ሳይሳኩ የቆየባቸውን ሶስት ምክንያቶች አብራርተዋል፡፡

በማብራሪያቸውም አንድ ክፍለ ዘመን በሚሻገረው የኦሮሞ ትግል ውስጥ ስትራቴጂካዊ ንድፈ ሃሳብ አለመኖሩ የመጀመሪያ ምክንያት መሆኑን እና ትግሉን እንዳዘገየው ተናግረዋል፡፡

ምርታማ ለመሆን የምርት ግብዓቶች አስፈላጊ ቢሆኑም ዘር ከሌለ ግን ማምረት እንደማይቻል ሁሉ፣ በኦሮሞ ትግል ውስጥ ጥያቄዎች ቢኖሩም ጥያቄዎች እንዲመለሱ ስትራቴጂ ነድፎ እና አቅምን አዘጋጅቶ መሄድ ላይ ችግር እንደነበር አውስተዋል፡፡

በሁለተኛ ደረጃ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ የነበሩ ልዩነቶች የኦሮሞ ትግል እንዲዘገይ ማድረጋቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በህዝቡ ዘንድ መረዳዳት እና ማንነቱን እና የትግሉን ጉዞ መረዳት ላይ ችግሮች እንደነበሩ አንስተዋል፡፡

በተለይም የኦሮሞ ሕዝብ በሰፊ ጂኦግራፊ መሬት ላይ የሚገኝ መሆኑ እንዲሁም የተለያዩ እምነቶች እና የፖለቲካ አመላካከቶች መኖራቸው የኦሮሞን ትግል ወደ ኋላ ሲጎትቱ ነበር ብለዋል፡፡

ትግሉ እዚህ ላይ ደርሶ እና አብዛኛው የኦሮሞ ጥያቄዎች ተመልሰው እንኳን መጥፎ አመለካከቶች እና የፖለቲካ ሴራዎች በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ መለያየትን እየፈጠሩ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡

እንደ ኦሮሞ ስንፈልግ በወንዝ፣ ስንፈልግ በእምነት፣ ስንፈለግ በዞን መለያያችን ብዙ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒሰትሩ÷ አሮሞ አንድ ቤተሰብ ሆኖ ሳለ ትንንሽ ነገሮችን በውይይት መፍታት ስንችል ክፍፍል እንፈጥራለን ብለዋል፡፡

የኦሮሞ ሕዝብ ልዩነቶች ቢኖሩትም እንደቤተሰብ ይመክራል እንጅ ለፖለቲካ ሴራ መጋለጥ የለበትም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ የጠላት መሳሪያ ሆነን አንድነታችን እየላላ ከሄደ የጠላት ፍላጎት እየተሳካ የኛ ድል ደግሞ እየራቀ ይሄዳል ነው ያሉት፡፡

ከተቃራኒ ሀይሎች ጋር ሩቅ መጓዝ የማይችል እና ከስትራቴጅካዊ የኦሮሞ ፍላጎት የራቀ ግንኙነት መፈጠሩ ሌላኛው የኦሮሞ ትግል ችግር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ጓደኛ ስትመርጥ ፀባዩን ባህሪውን ታያለህ እንጂ ዝም ብለህ አትመርጥም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከተቃራኒ ሀይሎች ጋር የሚደረግ ግንኙነት ስትራቴጂክ ካልሆነ የትግሉ ዓላማ ላይሳካ እንደሚችል አብራርተዋል፡፡

እነዚህ ችግሮች በኦሮሞ ትግል ውስጥ ሲታዩ የቆዩ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

  🇺🇸  አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው።የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺ...
01/08/2026

🇺🇸

አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺህ ዶላር ወደ 20 ሺህ ዶላር (3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) ከፍ በማድረግ ቋሚ ሊያደርግ ነው።

መሥሪያ ቤቱ እንደገለፀው መርሃ ግብሩ የቢዝነስ እና የቱሪስት (ቢ1 እና ቢ2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው።

ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ አሜሪካ ውስጥ ከቆዩ ገንዘቡ ተመላሽ እንዳይሆን የሚያደርገው ይህ አሠራር ተግባራዊ ይሆንባቸዋል ከተባሉ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ከሆኑ 50 አገራት መካከል ፦
- #ኢትዮጵያ፣
- ጂቡቲ፣
- ናይጄሪያ፣
- ሴኔጋል፣
- ኡጋንዳ፣
- ታንዛኒያ ይገኙበታል።

ይህ በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የተሻሻለው ፕሮግራም፣ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኝዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በመርሃ ግብሩ መሠረት አመልካቾች እንደ ኤምባሲው ኦፊሰሮች ውሳኔ ለቪዛ እስከ 20 ሺህ ዶላር (ከ3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) የሚደርስ ገንዘብ እንዲያስይዙ ሊጠይቁ ይችላሉ።

አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት የቪዛ ማስያዣ የሙከራ መርሃ ግብር ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ነበር።

መርሃ ግብሩ ለአንድ ዓመት የሚቆይ የነበረ ሲሆን የተቀመጠለት ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው አዲሱ መመሪያ የወጣው።

በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ቋሚ እንደሚሆንም ተገልጿል።

በተጠናቀቀው የሙከራ መርሃ ግብር መሠረት አመልካቾች ከ5 ሺህ ፣ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ እንዲያስይዙ ይጠየቁ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ፕሮግራም አነስተኛው 5 ሺህ ዶላር ከዝርዝሩ ወጥቶ፣ ከፍተኛው የማስያዣ ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ከፍ ተደርጓል።

በአዲሱ መርሃ ግብር ከተካተቱ 50 አገራት መካከል 30ዎቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው።

መረጃውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪታ ቤትን ዋቢ በማድረግ የዘገበው ቢቢሲ ነው።

ኢትዮጵያ
ሃምሌ 25 ቀን 2018 ዓ/ም

የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በጥቂት የህ...
01/08/2026

የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በጥቂት የህወሓት ፖለቲከኞች ተገፋፍተው ክልሉን ዳግም ወደ እልቂት ከመክተት እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።

አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት „አራት ኪሎ እንመለሳለን“ በማለት የሚያልሙትን „ቅዠት“ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።

ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። የሰራዊቱ ዋነኛ ትኩረት የትግራይ ህዝብ ሰላምና ህልውና እንጂ በጣት የሚቆጠሩ „ወንጀለኞች“ ህልውና ሊሆን እንደማይገባው አጽንኦት ሰጥተዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል ‚ይበቃል‘ ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመጨረሻም „በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን“ ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው „ዓለም ይድረስልኝ“ እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል።

 ሀዋሳ ከተማ በቤንዚን ተጠቃሚ ባለ 3 እግር ባጃጅ እና በኪዩት ባጃጅ ታክሲዎች እንቅስቃሴ ላይ አዲስ የትራፊክ ስምሪትና የመንገድ ክልከላ ተግባራዊ ሊሆን ነው።የሀዋሳ ከተማ ትራንስፖርትና መ...
31/07/2026



ሀዋሳ ከተማ በቤንዚን ተጠቃሚ ባለ 3 እግር ባጃጅ እና በኪዩት ባጃጅ ታክሲዎች እንቅስቃሴ ላይ አዲስ የትራፊክ ስምሪትና የመንገድ ክልከላ ተግባራዊ ሊሆን ነው።

የሀዋሳ ከተማ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ከከተማ ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር፣ " በከተማዋ የትራፊክ መጨናነቅን ለመቀነስና የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ያለመ " አዲስ የትራንስፖርት ስምሪት እና የመንገድ ክልከላ እንደሚጣል አስታውቋል።

አዲሱ አሰራር ከነገ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።

አዲሱ የትራንስፖርት ስምሪት፣ ዝግ የሆኑ መንገዶች እና አማራጭ ማቋረጫ መንገዶች የሚከተሉት ናቸው።

1ኛ) ለኪዩት ተሽከርካሪዎች ዝግ የሆኑ መንገዶች

➡️ ከሼል እስከ ቀድሞ ማዘጋጃ አደባባይ (መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን)
➡️ ከዋርካ አደባባይ እስከ አሮጌ ገበያ (የቀድሞ ግሎባል ጋራጅ) ድረስ ባለው አዲሱ የኮሪደር መንገድ
➡️ በዋናው ሀገር አቋራጭ መንገድ (ዋናው ሃይ ወይ) ... በነዳጅ የሚሰሩ ባጃጆችና ኩይት ታክሲዎች መንቀሳቀስ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ነው።

2ኛ) በነዳጅ ለሚሰሩ ባለ 3 እግር ባጃጆች የተከለከሉ መንገዶች

➡️ ከሜምቦ እስከ አዲሱ መናኸሪያ
➡️ ከአቶቴ (ዋርካ) በቦሌ መብራት እስከ አሊቶ ት/ት
➡️ ከሳውዝ ስፕሪንግ ሆቴል በመድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን አድርጎ እስከ 05 አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ድረስ ... ሙሉ በሙሉ ለባጃጅ ተሽከርካሪዎች ዝግ ይሆናሉ።

አማራጭ ማቋረጫ መስመሮች ፦

🟢 ከሼል እስከ የድሮ ማዘጋጃ አደባባይ (መድኃኒዓለም) ባለው የማቋረጫ መንገዶችን በተመለከተ ፦

👉 ባጃጅም ሆነ ኪዩት ተሽከርካሪዎች፦
- ከሼል- በቶታል ማደያ በኩል አድርጎ ወደ ጋሻው ጋራጅ፤
- በየሺ መብራት አድርጎ ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚወስደው መንገድ፤

👉 ኪዩት ብቻ፦
- በብሉናይል- በአዳነ ግርማ ወደ ኮሬም ሜዳ መስመር፤
- ከፒያሳ ዳሽን ወደ ሞቢል መስመር፤

🟡 ከአቶቴ ወደ አሊቶ መስመር ፦
- ቦሌ መብራት ማቋረጫ
- ከጉዱማሌ ፓርክ በኮብልስቶን

🔴 ከሜምቦ እስከ አዲሱ መናኸሪያ ድረስ ባለው መንገድ 7 ማቋረጫዎች ያሉ ሲሆን ፦
- ዩኒየን ትምህርት ቤት፣
- ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን፣
- ወጣቶች ማዕከል (ሰላም ራዕይ ዓለምአቀፍ ቸርች)፣
- ንግሴተ ፉራ ትምህትርት ቤት (አንተናውጋ)፣
- አላሙራ ትምህርት ቤት፣
- ታሪኩ ሕንፃ (አዲሱ ገበያ መግቢያ) እና
- ዐባይ የጥርስ ሕክምና

የባለ ሶስት እግር ቤንዚን ተጠቃሚ ባጃጆች እንዲሁም የኪዩት አሽከርካሪዎች ይህን አውቀው በተጠቀሱ መስመሮች ብቻ እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ሀዋሳ
ሃምሌ 24 ቀን 2018

የኢትዮጵያ የከፍታ ግስጋሴ በየትኛውም ኃይል አይገታም! ***************** ኢትዮጵያ ዛሬ በልጆቿ ጥልቅ አስተውሎት፣ በረቀቀ ጥበብ እና በሰከነ መስተጋብራዊ ምክር ያለፉ ዘመናት ታሪካ...
17/07/2026

የኢትዮጵያ የከፍታ ግስጋሴ በየትኛውም ኃይል አይገታም!
*****************

ኢትዮጵያ ዛሬ በልጆቿ ጥልቅ አስተውሎት፣ በረቀቀ ጥበብ እና በሰከነ መስተጋብራዊ ምክር ያለፉ ዘመናት ታሪካዊ ዕዳዋን በጥበብ በመደመር እያካካሰች ትገኛለች።

የወደፊቱን ብሩህ እና ደማቅ ዘመን ለማምጣት የትጋት ስንቅ ታጥቃ፣ የጽናት ቀበቶ ታጥቃ በቁርጠኝነት ተነሥታለች።

ትናንትን በይቅርታ እና በእውነት እያረመች፣ ነገን በታላቅ ተስፋ እና አዲስ ራዕይ እየገነባች፣ ዛሬን ደግሞ በብርቱ ሥራ እና በላብ ጠብታ እየተረማመደች ወደፊት ግስጋሴዋን በአስተማማኝ ሁኔታ አጠንክራ ቀጥላለች።

በታሪኳ ያጋጠሟትን፣ ያጎበጧትን እና ወደ ኋላ የጎተቷትን ውስብስብ ተግዳሮቶች እና ፈተናዎች ወደ ታላቅ የዕድገት መወጣጫ ዕድል በመቀየር፣ በሁሉም አቅጣጫ አዲስ የትንሣኤ ምዕራፍ ከፍታ ማፍጠን ጀምራለች።

ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን የፖለቲካ ስብራቷን፣ የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ድቀቷን እና ሥር የሰደደውን የማኅበራዊ ምስቅልቅሏን በጥበብ እያከመች አዲስ ሀገራዊ መሠረት እየጣለች ነው።

ፖለቲካዋን ሁሉንም አሳታፊ በሆነ ሀገራዊ ምክክር እና የጋራ መግባባት፣ ኢኮኖሚዋን ለኢትዮጵያ ምድር እና ነባራዊ ሁኔታ በሚመጥን የሀገር በቀል የልማት ቀመር፣ እንዲሁም ማኅበረሰባዊ እና ሥነ ልቦናዊ ቁስሏን በጥልቅ የመደመር እሳቤ እና ፍልስፍና በማከም ነገን አሻግራ እየተንቀሳቀሰች ትገኛለች።

ይህ የኢትዮጵያ ደማቅ ማንሰራራት እና የልዕልና ጉዞ ግን ለወደቁ እና የታሪክ ኪሳራ ለገጠማቸው ኃይሎች በፍጹም ሊዋጥላቸው አልቻለም፤ ወደፊትም አይዋጥላቸውም። ሕልውናቸውን በኢትዮጵያ ውድቀት፣ በመከራዋ እና በትርምስ ውስጥ ብቻ ለማግኘት የሚሞክሩ እና ሌሊት ተቀን የሚታገሉ እነዚህ የጥፋት ኃይሎች፣ የዛሬው የኢትዮጵያ ማንሰራራት ለእነሱ የሞት አዋጅ ሆኖባቸዋል።

የኢትዮጵያ ከፍታ እና በጽኑ መሠረት ላይ መቆም ለጎረቤትም ሆነ ለቀጣናው ሀገራት፣ አልፎም ለመላው አፍሪካ ታላቅ ትሩፋት እና በረከት መሆን ሲገባው፣ በአንዳንዶች ዘንድ እንደ ከባድ ስጋት ተመልክቷል።

በእውነታው ሚዛን እና በታሪክ መነጽር ሲታይ ግን፣ የኢትዮጵያ ማንሰራራት እና ጠንካራ መሆን ለሁሉም የጋራ በረከት ነው። ኢትዮጵያ የቀጣናው ኃያልና ጥንታዊ ባለታሪክ ሀገር፣ የአፍሪካ አንኳርና የጥቁር ሕዝቦች አሰባሳቢ እናት፣ የቀጣናው የፖለቲካና የደኅንነት ልዕልና ማዕዘን፣ እንዲሁም መተኪያ የሌላት ግዙፍ ምሰሶ ናት።

እሷ ስትረጋጋ ቀጣናው በሙሉ ይረጋጋል፤ እሷ ስታድግ አካባቢው ያብባል፤ እሷ ስትከበር አፍሪካ በዓለም መድረክ ትኮራለች። የኢትዮጵያ ጥንካሬ የሌሎችን ደኅንነት የሚያረጋግጥ እንጂ፣ በማንኛውም መለኪያ ስጋት ሊሆን አይችልም።

ይህች የቀጣናው ግዙፍ ሀገር፣ የራሷን ዜጎች አልፎ ጎረቤቶቿን በኢኮኖሚ ትስስር፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታና በሰላም ማስከበር ተልእኮዎች እያገለገለች ትገኛለች። በመሆኑም የኢትዮጵያ ብልጽግና የቀጣናው ብልጽግና መሆኑን መገንዘብ ግድ ይላል።

ይህንን ሐቅ መቀበል ያቃታቸው፣ እነዚህ ጥቂት የከሸፉ ቡድኖች የኢትዮጵያ ማገር መጽናት፣ ማበብ እና መታደስ ክፉኛ አስበርግጓቸዋል። ሀገራችን የተያያዘችውን እና የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ በማንኛውም መንገድ ለማስቆም በየጓዳው፣ በየአደባባዩ እና አልፎም መስጊድ እየታደሙ የሴራ ድር ይሸምናሉ።

ይሁን እንጂ፣ ይህ ያረጀ እና ያፈጀ የጥፋት ጥረታቸው ከ"የሞት ጣዕር መንፈራገጥ" የዘለለ ምንም ዓይነት ትርጉምም ሆነ ውጤት ሊኖረው አይችልም። ኢትዮጵያን አሁን በፍጥነት ከምትገሰግስበት የለውጥና የዕድገት ሐዲድ ላይ ለሰከንድ እንኳን ጋብ ሊያደርጋት አይችልም።

የ2018 የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊው ሲዳማ ቡና የቡድን አባላት ሽልማት ተበረከተላቸውየ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ለሆ...
13/07/2026

የ2018 የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊው ሲዳማ ቡና የቡድን አባላት ሽልማት ተበረከተላቸው

የ2018 የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ አሸናፊ ለሆነው የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ በዛሬው ዕለት በሀዋሳ ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

ከአቀባበሉ በኋላም ማምሻውን በሀይሌ ሪዞርት በተደረገ የእራት ግብዣ ላይ ዳጎስ ያለ ሽልማት ተበርክቶለታል። የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ፣ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ፣ አቶ በየነ በራሳ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የስፖርት ምክር ቤት ሰብሳቢ ፣ አቶ አብርሃም ማርሻሎ የክልሉ የመንግስት ተጠሪ እና የብልፅና ቢሮ ሀላፊ ፣ አቶ ጃጎ አገኘሁ የክልሉ የባህል ፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ እና የክለቡ የቦርድ ሰብሳቢ እና ሌሎች የመንግስት ሀላፊዎች እና የክለቡ አመራሮች በርካቶች ጥሪ የተደረገላቸው እና የክለቡ አባላት በተገኙበት ሽልማት ተበርክቷል።

ለአሰልጣኝ ያሬድ ገመቹ እና ለረዳት አሰልጣኙ ቅዱስ ዘሪሁን እንዲሁም ለህክምና ባለሙያው ብሩክ ደበበ ሀዋሳ ከተማ ላይ የ200 መቶ ካሬ መሬት ከነ ካርታው እና የ1 ሚሊዮን ብር ሲሸለሙ ለያሬድ ባዬ ፣ ደስታ ደሙ ፣ ብርሀኑ በቀለ ፣ ደግፌ አለሙ ፣ ዮሴፍ ዮሐንስ ፣ ሬድዋን ናስር ፣ መስፍን ታፈሠ ፣ አስቻለው ሙሴ ፣ ፍቅረየሱስ ተወልደብርሃን የ2 መቶ ካሬ መሬት እና 1 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ለቀሩት ተጫዋቾች የ2 መቶ እና የ150 ካሬ የመሬት እንዲሁም ለቀሩት የቡድኑ ተጫዋቾች ለሾፌር ለረዳት እንዲሁም ለሌሎች አካላት የገንዘብ ሽልማት ተበርክቷል።

እንዲሁም ክለቡ እዚህ እንዲደርስ ላደረጉት የቀድሞው ስራ አስኪያጅ አቶ መንግሥቱ ሳሳሞ የእውቅና እና የ2 መቶ ሺህ እንዲሁም ደግሞ ለክለቡ አስጨፋሪ እያሱ ሲዳ የ2 መቶ ካሬ መሬት ለክለቡ ደጋፊ ማህበር እና ለክልሉ እግር ኳስ ፌድሬሽን በተመሳሳይ የ2 ሚሊዮን ብር እና ለሌሎችም የመሬት የገንዘብ እና የሰርተፊኬት ሽልማት ከተበረከተ በኋላ መርሃግብሩ ተጠናቋል።

ስፔን ኦስትሪያን 3-0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች አለፈች  | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ32 ዙር ጨዋታ ስፔን ኦስትሪያን 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች ማለፍ ችላለች። ጨዋታው በአ...
02/07/2026

ስፔን ኦስትሪያን 3-0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች አለፈች

| በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ የ32 ዙር ጨዋታ ስፔን ኦስትሪያን 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች ማለፍ ችላለች። ጨዋታው በአሜሪካ ሎስ አንጀለስ ተካሂዷል።

ለስፔን ሚካኤል ኦያርዛባል ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ፔድሮ ፖሮ አንድ ግብ ጨምሯል። ማርክ ኩኩሬያም ለሁለቱ ግቦች የመጨረሻ ኳስ በማቀበል በድሉ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል።

በዚህ ውጤት ስፔን በቀጣዩ ዙር ከፖርቱጋል እና ክሮኤሺያ አሸናፊ ጋር ለሩብ ፍጻሜ መግቢያ ትፋለማለች። ኦስትሪያ በበኩሏ ከ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር ተሰናብታለች።

ስፔን በዚህ ውድድር እስካሁን ያሳየችውን ጠንካራ አቋም በመቀጠል ለዋንጫው ከሚፎካከሩ ጠንካራ ቡድኖች መካከል መሆኗን አረጋግጣለች።

Address

ሂጣታ
Awassa

Telephone

+251919540760

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alte pictures posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Alte pictures:

Shortcuts

Share

Category