07/06/2026
በጉራጌ ዞን የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የወልቂጤ ምርጫ ክልል ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ ።
#ወልቂጤ| ግንቦት 30/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን የ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ የወልቂጤ ምርጫ ክልል ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት ይፋ ሆኗል ።
የወልቂጤ ምርጫ ክልል አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሲሳይ ጀማል ግንቦት 24/የተደረገው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም መጠናቀቁን ገልፀዋል።
በወልቂጤ የምርጫ ክልል ውስጥ 141 የምርጫ ጣቢያዎች እንደነበሩ ገልፀው ከድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኃላ 141 የምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ወረቀቶች ተሰብስቦ የማጠቃለል ስራ ሲሰራ እንደነበረ ተናግረዋል ።
በዛሬው ዕለትም ጥቅል ውጤቱን የማጠቃለል ስራ በማጠናቀቅ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ መደረጉን ገልፀዋል።
በዚህም በምርጫ ክልሉ ውስጥ 166,589 ህዝብ የምርጫ ካርድ እንደወሰዱ ገልፀው ከዚህ ውስጥ 156,291 ህዝብ ድምፅ እንደሰጠ ገልፀዋል።
በዚህም መሠረት በወልቂጤ ምርጫ ክልል
✅ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ከቀረቡት መካከል የተመዘገበው ውጤት
👉ሙአዝ በድሩ ሁሴን(ዶክተር) ብልፅግና ፓርቲ =142,456
👉መሀመድ አብራር መሀመድ ጎጎት ለጉራጌ አንድነት ፓርቲ =5198
👉መስፍን አበራ አብዛ ከነጻነትና እኩልነት ፓርቲ= 692
👉ደምስ ገብሬ መረቶ ከኢዜማ ፓርቲ=2211
👉ኢክራም ሰይፍ በሽር ከወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ= 547
👉አዲሱ ደቀባሽ አበበ ከወሎ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ=380
👉እንዳለ ኤርገንዶ ጥሊቦ ከትብብር ለኢትዮጵያ=439
ድምፅ ማግኘታቸውን ተገልጿል።
✅ለክልል ምክር ቤት
📌 ሙራድ ከድር መሀመድ ብልፅግና ፓርቲ =144,751
📌ዙልፋ አለዊ ነጋሽ ብልፅግና ፓርቲ = 142,850
📌ኢንጂነር ካሳዬ ተክሌ ስራ ብልፅግና ፓርቲ =142,367
📌መሀመድ አሚን በደዊ ነጋሽ ብልፅግና ፓርቲ =142,262
📌ካሱ ጁሀር ስንክርታ ብልጽግና ፓርቲ=142,071
📌ሳራ ጀማል ሻፊ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ=1,269
📌ሰማን አብድላ አህመድ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ=1,113
📌ማእረግ ፍቃዱ ናማጋ ጎጎት ለጉራጌ አንድነት ፍትህ ፓርቲ =2,833
📌ፍቃዱ ጠንክር ኬራጋ ጎጎት ለጉራጌ አንድነት ፍትህ ፓርቲ= 2,803
📌አንተነህ ኮሬ አጨ ጎጎት ለጉራጌ አንድነት ፍትህ ፓርቲ= 2,514
📌አብድላዚዝ ሙሰማ ሀሰን ጎጎት ለጉራጌ አንድነት ፍትህ ፓርቲ= 2,279
📌ሂክማ አብራህማን አረጋ ኢዜማ ፓርቲ= 2,162
📌አንተነህ ተስፋዬ ገ/ስላሴ ኢዜማ ፓርቲ= 2,446
📌ዳንኤል ኸ/ጊዮርጊስ ወጋየሁ ኢዜማ ፓርቲ= 2,172
📌ፈድሉ አህመድ በሽር ኢዜማ ፓርቲ= 1,981
📌ሙሀባ ግራኝ ሻፊ ከወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ= 905
📌አህመድ ጀማል ማረኝ ከወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ= 497
📌ሙክታር መኪ ነጋሽ ከወለኔ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ= 283
ድምፅ መሆኑን ጊዜያዊ የወልቂጤ ምርጫ ክልል ውጤት ያሳያል።
ዘገባው የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።