26/07/2024
ወንድም ዶ/ር በለጠ ሽኩሮ የወርቅ ኒሻንና ዲፕሎማ ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል!
===========================
የአቢሲኒያ የኢንደስትሪ ሽልማት ድርጅት የአለርት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማሀበራዊ ዘርፍ ህዝቡን በቅንነት በማገልገል ላበረከተው አስተዋፅኦ እና ለሃገርና ለህዝብ የሚጠቅም አገልግሎት በመስጠቱ የ2016 ዓ.ም የአቢሲኒያ የወርቅ ዋንጫና ዲፕሎማ ሲሸልም የቀዶ ጥገና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር በለጠ ሽኩሮ የወርቅ ኒሻንና ዲፕሎማ ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል!
በላቀ አገልግሎትህ አኩርተንሃል! እንኳን ደስ አለህ!
Via Habtamu Taye Belete Shikuro