Yeka Woreda 07 Communication

Yeka Woreda 07 Communication Yeka Sub City Wereda 07 Communication Is a 24 Hour Working Public Medical 🌍

09/06/2026

የካ መሶብ

በትናንትናው ዕለት በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተገንብቶ የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ባለሰባት ወለል ህንፃ ማዕከል በአንድ ጊዜ 96 ተገልጋዮችን ማ...
09/06/2026

በትናንትናው ዕለት በየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ተገንብቶ የተመረቀው መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት መስጫ ባለሰባት ወለል ህንፃ ማዕከል በአንድ ጊዜ 96 ተገልጋዮችን ማስተናገድ የሚችል፣የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎቶች የሚሰጥ ሲሆን በውስጡ የመንግስት ሰራተኞች የህፃናት የቀን ማቆያ ማዕከል፣መሰብሰቢያ አዳራሾች እና የሰራተኛ ካፍቴሪያ ያሟላ ነው።

08/06/2026
የወንዞች ዳርቻዎች ልማት የኢኮኖሚ መነቃቃትንና የሀገር ውስጥ አቅምን እየገነባ ነውበአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የወንዞች ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክቶች ከተማዋን ውብ እና ከብክለት ነፃ ...
08/06/2026

የወንዞች ዳርቻዎች ልማት የኢኮኖሚ መነቃቃትንና የሀገር ውስጥ አቅምን እየገነባ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የወንዞች ዳርቻዎች ልማት ፕሮጀክቶች ከተማዋን ውብ እና ከብክለት ነፃ ከማድረግ ባለፈ ዘርፈ ብዙ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎችን እያስገኙ ይገኛሉ፡፡

በከተማዋ ከእንጦጦ ተራራ ተነስቶ እስከ አቃቂ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ድረስ የሚዘልቅ የ56 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ግዙፍ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በተለያዩ ምዕራፎች ተከፋፍሎ እየተተገበረ ነው፡፡

ለአብነትም ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ፣ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፤ ከወንዞቹ ዳርና ዳር እስከ 50 ሜትር እንደሚዘልቅ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

ፕሮጀክቱ የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያና የመዝናኛ ስፍራዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ እንዲሁም የንግድ እና የከተማ ግብርና ማዕከላትን አቀናጅቶ የያዘ ነው፡፡
ከዚህ ቀደም መሰል ግዙፍ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በዋናነት በውጭ ሀገር ባለሙያዎችና አማካሪዎች የሚሰሩ የነበሩ ናቸው፡፡

ይሁን እንጂ የእነዚህ አዳዲስ ፕሮጀክቶች የንድፍ (ዲዛይን) እና የትግበራ ስራዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች የተቀረጹና የተተገበሩ በመሆናቸው፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት ያላቸውን የመፈጸም አቅምና ብቃት በተግባር አሳይቷል፡፡

በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ እና በአርክቴክቸር፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስና ተያያዥ የሙያ መስኮች ለበርካታ ዜጎች አዲስ የስራ ዕድል በመፍጠር የሀገር ውስጥ የኮንስትራክሽን ዘርፍን በከፍተኛ ደረጃ ማነቃቃት ችሏል፡፡

ከአረንጓዴ ኮሪደሮችና ከመዝናኛ ስፍራዎች ጎን ለጎን የከተማ ግብርና እና የንግድ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው ለነዋሪዎች ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ማስገኘታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

ቀደም ሲል በቆሻሻ መጣያነትና ለጎርፍ አደጋ ስጋት የነበሩት የወንዝ ዳርቻዎች አሁን ላይ ለሽርሽር ምቹ ፣ ለሸማቾችና ለነጋዴዎች በቀላሉ መገበያየት የሚያስችሉ፣ ደህንነታቸው የተጠበቀና ማራኪ የገበያና የመዝናኛ ማዕከላት ሆነዋል፡፡

06/06/2026
06/06/2026
‎የወረዳዉ ጠቅላላ አመራር እየተሰሩ ያሉ መደበኛ የፓርቲ እና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም እና ቀጣይ በልዩ  በትኩረት የሚሰሩ ተግባራትን አስመልክቶ ከጠቅላላ አመራር ጋር ውይይት ተደረገ ። ...
05/06/2026

‎የወረዳዉ ጠቅላላ አመራር እየተሰሩ ያሉ መደበኛ የፓርቲ እና የመንግስት ስራዎች አፈፃፀም እና ቀጣይ በልዩ በትኩረት የሚሰሩ ተግባራትን አስመልክቶ ከጠቅላላ አመራር ጋር ውይይት ተደረገ ።
==========================
Yeka Woreda 07 Communication
‎
ዛሬ ‎የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር የወረዳው አጠቃላይ አመራር በተገኘበት

👉የሞዴል ብሎክ ግንባታ

👉 አገልግሎት አሰጣጥ

👉የመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ

👉 የተለያዩ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም

👉የስራ ዕድል ፈጠራ እና

👉 አጠቃላይ የውስጠ ፓርቲ ስራዎች ገምግሟል።

‎የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጥሩአለም ባሳዝነው እንደገለፁት እነዚህ ተግባራት ሁሉም አመራር ርብርብ የሚያደርጉባቸው መሆኑንና እያንዳንዱ ተግባራት በታቀደላቸው ቀናት መስራት እንደሚገባ በመግለፅ የስራ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን ።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ደራራ ጫልቺሳ በመደመር መርህ ተግባራትን መፈፀም እንደሚገባ በመግለፅ በጋራ ለላቀ ውጤት ያበቃል ያሉትን የስራ ስምሪት በመስጠት ተጠናቋል ።

ግንቦት 28/2018 ዓ.ም
!

fore more information
👇👇👇👇👇👇👇👇👇✅
https://linktr.ee/yw7commm

01/06/2026

ምርጫው ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተካሄደ ነው - የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና ነጻ በሆነ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አስታወቀ።

ምክር ቤቱ ይህንን የገለጸው በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በተቋቋመውና የምርጫ ሂደቱን በቀጥታ በሚከታተልበት የክትትል ክፍል በሰጠው መግለጫ ነው።

በመግለጫው፤ መራጩ ሕዝብ የዴሞክራሲ ሥርዓት እንዲሰፍን ከፍተኛ ጨዋነት በተሞላበት መልኩ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ጀምሮ ከቤቱ በመውጣት ድምፅ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሶ ለዚህም ምስጋና አቅርቧል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች አማራጭ ሐሳባቸውንና ርዕዮተ-ዓለማቸውን በመገናኛ ብዙኃን አማካኝነት ካስተዋወቁ በኋላ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ ለመራጭነት መመዝገቡን ያስታወሰው ምክር ቤቱ፣ ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ባለው ሂደትም ሂደቱ ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ መዋሉን ገልጿል።

ምክር ቤቱ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ባለው መዋቅር አማካኝነት መረጃዎችን ሲለዋወጥና ሂደቱን ሲከታተል እንደነበር የጠቆመ ሲሆን፤ እስካሁን ባለው ሂደት የጸጥታ አካላት፣ ታዛቢዎች እንዲሁም በጎ ፈቃደኞች እያደረጉ ባለው ገለልተኛ አገልግሎት መደሰቱንም አስታውቋል።

በቀሪው የድምፅ አሰጣጥ ሂደትም ህዝቡ እስካሁን ባለው ጨዋነትና ትዕግሥት የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጋራ ምክር ቤቱ ጥሪውን አቅርቧል።

01/06/2026

Address

Around Signal Kibeb (101m)
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yeka Woreda 07 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yeka Woreda 07 Communication:

Share

Category