15/06/2025
የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን ግን ምን እየሰራ ነው?
በ 50 ቢልዮን ብር የተገነባው የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ እየበሰበሰ ፣ አየዛገ እና እየወደመ ይገኛል። እንደዚህ ስል ብዙ ሰዎች ብዙ ነገር ሊሉ ይችላሉ። የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ የኢትዮጵያ ሀብት ነው ወይ ደግሞ በብድር የተሰራ የኢትዮጵያ ዕዳ ነው። ሰላም ሳይኖር አንተ ስለ እድገት ታወራለህ የሚል አይጠፋም ከ ከተሞች ኮሪደር ፕሮጀክት ይልቅ አንድ ግዙፍ የስኳር ፋብሪካ ለአንዲት ሀገር እጅግ ጠቃሚ ነው። ሲቀጥል ፋብሪካዎች ከሌሉ ከተሞች ምንም አይደሉም።
ንሮ እንዲከብዱ ካደረጉ ነገሮች አንዱ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ፋብሪካዎች ስራቸውን በማቆማቸው ነው።
እርግጥ ነው በዚህ አምስት ዓመት ውስጥ ብዙ ፋብሪካዎች ስራቸውን እንዳቆሙ የሚታወቅ ነው። ነገር ግን የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ ከግዙፉነቱ እና ከጨረሰው በጀት አንፃር እንዲሁም ከሚሰጠው ጥቅም አንፃር ሲታይ 90 ፐርሰንት አልቆ እያለ ኮርፖሬሽኑ ስራው ከመስርሳቱ የተነሳ እየወደመ ፣ እየዛገ እና እየበሰበሰ መገኘቱ ነው። አይደለም የ አምሳ ቢልዮን ብር ወይም ተገዢ የሆንለትን የ4.5 ቢልዮን ዶላር ፕሮጀክት ይቅርና የአምስት መቶ ሺ ፕሮጀክትም እልባት ሳይሰጠው እንዲሁ ባክኖ አይቀርም ነበር። አምሳ ቢልዮን በቆየ ዋጋ ነው በአሁኑ ቢሆን ስንት ይሆን እንደነበር መገመት አይከብድም፣ ፋብሪካው ከተጀመረ አስር ዓመት አልፎታልና።
ኢትዮጵያ በሺዎች አልያም በሚልዮኖች ኩንታል ስኳር ከ ህንድና ሌሎች አገሮች ታስገባለች ታድያ ለዚህ መፍትሔው ያለቀው ግዙፍ ፋብሪካ ስራ ማስጀመር ፣መጠበቅ እና መንከባከብ ሲገባ አላውቀውም ተብሎ አምስት ዓመት ዝም ማለት ይገባ ነበር?
ሕዝቡ የሚጠብቀው ሌላ አዲስ ፋብሪካ እንዲገነባ ነው ካልሆነ ግን የተሰራውን መጨረስ እና ማደስ ያቆመውን እንዲጀምር ግን በብዙዎች ኢትዮጵውያን የሚጠበቅ ነው።
የማያውቁ ይመስልሀል? የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል። ልክ ነው አውቆ የተኛን መቀስቀስ ከባድ ነው! ነገር ግን እንደተባለው እንዲሁ ከሆነ በዓለሙ ሁሉ ላይ ያሉ ሀገር ወዳድ ዜጎች ይመልከቱት ነው መልሱ።
እንደኔ የተሰማችሁ ሼር አድርጉት የሚመለከተው አካል መልስ እንዲሰጠው።
Wendmsew Abrha