የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሐገርም በላይ ናት

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሐገርም በላይ ናት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሐገርም በላይ ናት ለአንቺ የማይገዛ ሕዝብ እና መንግስት ይጠፋል እነዚያ አህዛብም ከተው ይጠፋሉ
ት.ኢ 60፥12

09/05/2026
26/04/2026
19/04/2026

With ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ – I'm on a streak! I've been a top fan for 20 months in a row. 🎉

17/04/2026

"ወንጌል ለሰላም፣ ሰላም ለሀገር" በሚል መሪ ቃል ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በኮንሶ ዞን ወረዳዎች ቤተ ክህነት በካራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ይካሄዳል።
፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
ሚያዚያ ፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሚዲያ- አርባ ምን

የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት ሥብከተ ወንጌል ጥምር ኮሚቴ እና የኮንሶ ዞን ወረዳዎች ቤተ ክህነት በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ “ወንጌል ለሰላም ወሰላም ለሀገር” በሚል መሪ ቃል በካራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ከሚያዚያ ፲፮ እስከ ፲፱ ቀን ፳፻፲፰ ዓ/ም ለተከታታይ አራት ቀናት ይካሄዳል ።

በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ ቡራኬና ትምህርት ለመስጠት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የሚገኙ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል፦ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የጋሞና አካባቢው፣ ጎፋና ባስኬቶ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በአሜሪካ የቴክሳስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሆናቸው ተረጋግጧል።

ከአዲስ አበባ የሚመጡት ታዋቂው ሰባኬ ወንጌል ሊቀ ሊቃውንት ዮሴፍ ደስአለኝ የሊቃውንት ጉባኤ አባልን ጨምሮ ሌሎች ዘማሪያን በጉባኤው ላይ ተገኝተው ያገለግላሉ።

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ገሪማ ጌታነህ ፣ ዋና ጸሐፊ መጋቤ ሰናያት ያዕቆብ ደስታ እንዲሁም የየክፍል ኃላፊዎች፣ በሀገረ ስብከቱ ሥር የሚገኙ የ፲፭ቱም ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣የከተማ፣ የወረዳና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ እንዲሁም አገልጋዮችና ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ማህበረ ምዕመናን ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኮንሶ ዞን ወረዳዎች ቤተ ክህነት ባስተላለፈው መልእክቱ፤ ይህ ጉባኤ ወንጌልን በማስፋፋት ለሀገር ሰላምና አንድነት ያለውን ፋይዳ በመገንዘብ፣ ምዕመናን ከየአቅጣጫው በመምጣት በረከቱን እንዲካፈሉ ጥሪውን አቅርቧል።

ይህንን ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ የሀገረ ስብከቱ ሚዲያ በቦታው በመገኘት አጠቃላይ የጉባኤውን ሂደትና መርሃ ግብሮች በቀጥታ ስርጭት (Live) በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ ኦርቶዶክሳዊያን ምዕመናን የሚያስተላልፍ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን።

ወንጌል ለሰላም ወሰላም ለሀገር!

ነቅዐ ጽድቅ የጋሞና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሚዲያ
▶️ፌስ ቡክ
https://www.facebook.com/profile.php?id=1

▶️ዩቱብ
https://www.youtube.com/

▶️ኢንታግራም
https://www.instagram.com/gamoha

▶️ቲክ ቶክ
tiktok.com/

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሐገርም በላይ ናት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share